ጥናት 1.1
ምዕራፍ 1:1-5
የጳውሎስ ሐዋርያነቱ ፡
o በኢየሱስ ክርስቶስ የሆነ
o በ እግዚአብሄር አብ የሆነ
o ከሰዎች ያልሆነ
o በሰዎች ያልሆነ
ጳውሎስ ገላትያ ክልልን ለቅቆ ከሄደ በኋላ ፈናቲክ(ኤክስትሪሚስት) “ጭፍን” አመለካከት ያላቸው አይሁዳውያን በቤት እምነቶቹ መግባታቸው በክርስቶስ እየሱስ የሚገኘውን ነጻ የጽድቅ ትምህርት በማጣመም በሃይማኖታዊ ጥበብ እና ስራዓቶች በመቀየጥ ንጹሁን ወንጌል መበረዛቸው ነበር መልዕክቱን ለመጻፍ ያነሳሳው።
ወንጌሉ በአነሳሱ ሃይማኖታዊ ስራዓቶችን እየደገፈ እያበረታታ የመጣ ሳይሆን ፈንቅሎ የወጣ እንግዳ ነገር ነው። በሃይማኖታዊና ማህበራዊ ስራዓቶች የነበረውን ተቀባይነት ያለው ድርጊት፤ ባህል እና ስምምነት የናደ ታላቅ አብዮት ነው። ወንጌሉ በዚህ ዓለም ክስ ቀርቦበታል። ወንጌሉን በ እግዚአብሄርና በሰው ላይ የተነሳ ምድርን የወረረ እጅግ ክፉ ወረርሽን ነው ትል ነበር አለም።
በሌላ መልኩ ወንጌሉ ለዓለም በክርስቶስ እየሱስ የሚሆንን ድነት ፤ የህሊና ሰላምን እና በረከትን አምጥቷል። ዓለም የጠላችው በዚህ ምክንያት ነው።
እነዚህ ወግ አጥባቂ ጭፍን አይሁዳውያን
- · ትክክለኛ የአብርሃም ነገድ መሆናቸውን
- · እውነተኛ የኢየሱስ ክርስቶስ አገልጋይ መሆናቸውን
- · በእውነተኞቹ ሃዋርያት የተማሩ መሆናቸው
- · ተዓምራትን ማድረግ እንድሚችሉ
· እነዚህ ሃሰተኞች የጳውሎስን ሃዋርያዊ ስልጣን ያጣጥሉ ነበር፤ ጳውሎስ የመጨረሻ እንደሆነ ከነሱ በታች እንደሆነ፤ ክርስቶስን እነሱ እንዳዩት እና በአካል እንድሚያውቁት ፤ ሲያስተምር ከአፉ እንደሰሙ ፤ መንፈስ ቅዱስን እንደተቀበሉ እና እንደማይሳሳቱ ፤ ጳውሎስ ቤተክርስቲያንን አሳዳጅ እንደነበረ ለረጅም ጊዜ ፤ እየሱስን እንዳላየው ፤ ከአይሁዳዊ ሃዋርያትም ጋር መልካም ግንኙነት እንደሌለው በገላትያ ክልል ላሉ አማኞች ይናገሩ ነበር።
Comments
Post a Comment