Posts

አዲሱ ንባብ

ጥናት 3 ማብራሪያ

ጥናት 3 ማብራሪያ  ይህ ጳውሎስ በተቃዋሚዎቹ   ለቀረበበት ክስ ምላሽ የሰጠበት ወሳኝ ሃሳብ ነው። ወንጌሉን ከሰው እንዳልተቀበለው ይልቅስ ከ እየሱስ ክርስቶስ ከራሱ በመገለጥ እንደተቀበለ እያስረዳ ነው። ወንጌሉ ሰዎች ያቀበሉት አልነበረም። ሰዎችም አላስተምሩኝም እያለ ነው። ከሰው አይደለም ሲል ጳውሎስ “ምድራዊ ወንጌል አይደለም ያለኝ”   እያለ ብቻ አይደለም ። ምክንያቱም ተቃዋሚዎቹም የ እኛ ወንጌል ሰማያዊ ነው ምድራዊ አይደለም ስለሚሉ ነው። ጳውሎስ እያለ ያለው በሰው እጅ ተጽፎ ፤ ከሰው እግር ስር ተቀምጬ   ወይም በሰው እርዳታ ተነቦልኝ ያገኘውት ወንጌል አይደለም እያለ ነው። ስለዚህ ከሰው አይደለም ሲል ሰው ድርሻውን አዋጥቶበት በሰው በኩልም እንደ ሰው የተሰጠኝ ወንጌል አይደለም እያለ ነው። ኢየሱስ ገልጦልኛል ሲል ወንጌሉን በልዩ መገለጥ ከ እየሱስ ክርስቶስ ከራሱ እንዳገኘው እየተናገረ ነው።   ጳውሎስ ወንጌሉን ወደ ደማስቆ እየተጓዘ ሳለ እየሱስ ሲገለጥለት ነበር የተቀበለው። ቅዱስ ሉቃስ በሓዋርያት ምዕራፍ 9 ላይ   እየሱስ ከርስቶስ ጳውሎስን ተነስ እንዳለው ወደ ከተማ እንዲገባ እንደነገረው እና ማድረግ ያለበትን ነገሮች እንደሚነገሩት ነግሮት ነበር። እየሱስ ክርስቶስ ጳውሎስን ወደ አናንያ ወንጌሉን እንዲማር አልነበረም የላከው። አናንያ ያደርገው ነገር ጳውሎስን ማጥመቅ እጁን እንደጫነበት ወደ ቤተ ክርስትያንም እንዲሆን እንደነገረው እናያለን።   እርሱ አናንያ ጳውሎስን ያለው ነገር “ ወንድማችን ጳውሎስ እየሱስን ላንተ እንደተገለጸልህ ለ እኔም ተገልጾ አይንህ እንደሚከፈትና በመንፈስ ቅዱስ እንደምትሞላ ነግሮኛል። ጳውሎስ ከ አናንያ መመሪያን አልተቀበለም!   ጳውሎስ በክርስ...

ጥናት -3 ጥያቄዎች

ጥናት -3  የጳውሎስ ሐዋርያነት (1:11-12) ወንድሞች ሆይ፥ በእኔ የተሰበከ ወንጌል እንደ ሰው እንዳይደለ አስታውቃችኋለሁ፤ ኢየሱስ ክርስቶስ ገልጦልኛል እንጂ እኔ ከሰው አልተቀበልሁትም አልተማርሁትምም።   ጥ ያቄዎች 1.        ጳውሎስ ስለተቀበለውና ስለሰበከው ወንጌል ምንንነት እንዴት ያስረዳል ?

ጥናት 2 መልሶች

 የጥናት ሁለት መልሶች ከማብራሪያ ጋር   ጳውሎስ እደነቃለው ሲል የተታለሉትን ገላትያውያን አማኞችን በዝግታ ሊመክር መጀመሩን አመላካች ነው። እደነቃለው ማለቱ ለእነርሱ ያለውን መልካም መገረም ለመግለጽ አይደለም። የጥሩ ክዋኔ ማበረታቻ ሳይሆን እንደውም እንዳፈረባቸው እና በተፈጠረው ሁኔታ ማዘኑን መቆጨቱን አመላካች ነው። የጳውሎስ ዓላማ ለገላትያ አማኞች ፡ ወደ እውነተኛው የዳኑበት መንገድ እንዲመለሱ በመሆኑ በዝግታና በፍቅር ይናገራቸው ይጀምራል። ምክንያቱም ፡   በጳውሎስ እሳቤ ማንም ቢሳሳት ወደ መልካሙ መንገድ የሚቀናው ወይም የሚስተካከለው በፍቅር እንደሆነ ያምናል ያስተምራልም። ሰዎችን ለመመለስ እየፈረዱ፤ እየጮሁ ፤እያጋጩ የመሄድን ዝንባሌ የጳውሎስ ንጹህ ወንጌል በትምህርቱ   አይደግፍም። ለተታለሉ ወገኖች ጥፋታቸውን ሳይሆን መመለሳቸውን መዳናቸውን ስለሚፈልግ በመልካም ንግግር በለዘበ አንደበት ንግግሩን “እደነቃለው “ በሚል የቁጭት እና የመሪር ሃዘን ቃል ይናገራቸዋል።   እነዚህን የገላትያ አማኞች ነድፈው የበከሉዋቸው ተንኮለኞች መኖራቸውን መዘንጋት ውስጥ አልገባም ጳውሎስ በመልክቱ ። ነገር ግን   ጳውሎስ በወንጌሉ ስብከት ያመኑትን ወገኖች እንደ ወላጅ በ እንክብካቤ መገሰጽን መርጧል። ዋናው ትኩረቱ እነሱን ማትረፍ በመሆኑ ነው። ጳውሎስ በፈተና ተሰናክለው ለወደቁ የሚራራ ቀና መንፈስን ተቀብሏል።   ስለ መንጋው እጅግ የሚገደው እረኛ ነበር። ቦታውንና ስሙን ለማስጠበቅ ሳይሆን ነፍሳትን ለማዳን ነበር ግቡ።    ነፍሳትን ለማዳን ነበር በብዙ ሺ የሚቆጠር ኪሎሜትሮችን በብዙ ስቃይ እና መከራ ተጉዞ ወንጌሉን በሚሲዮነነት ሲያዳርስ የነበረው። ለህይወቱ ሳይሳሳ የኖረለት ወንጌ...

ጥናት 2 ጥያቄዎች

ውግዘት (1:6-10) 6 በክርስቶስ ጸጋ እናንተን ከጠራችሁ ከእርሱ ወደ ልዩ ወንጌል እንዲህ ፈጥናችሁ እንዴት እንዳለፋችሁ እደነቃለሁ፤ 7 እርሱ ግን ሌላ ወንጌል አይደለም፤ የሚያናውጡአችሁ የክርስቶስንም ወንጌል ሊያጣምሙ የሚወዱ አንዳንዶች አሉ እንጂ። 8 ነገር ግን እኛ ብንሆን ወይም ከሰማይ መልአክ፥ ከሰበክንላችሁ ወንጌል የሚለይ ወንጌልን ቢሰብክላችሁ፥ የተረገመ ይሁን። 9 አስቀድመን እንዳልን እንዲሁ አሁን ሁለተኛ እላለሁ፥ ከተቀበላችሁት የተለየውን ማንም ቢሰብክላችሁ የተረገመ ይሁን። 10 ሰውን ወይስ እግዚአብሔርን አሁን እሺ አሰኛለሁን? ወይም ሰውን ደስ ላሰኝ እፈልጋለሁን? አሁን ሰውን ደስ ባሰኝ የክርስቶስ ባሪያ ባልሆንሁም።                                              ጥያቄዎች           ጳውሎስ እደነቃለው ማለቱ ምን ማለት ነው?          ልዩ ወንጌል ምን አይነት ነው?          የተረገመ ይሁን ማለት ምን ለማለት ነው?       የክርስቶስ ባሪያ ምን አይነት ባህሪ አለው?  

ጥናት 1.1

Image
    ምዕራፍ  1:1-5 የጳውሎስ  ሐዋርያነቱ ፡ o     በኢየሱስ ክርስቶስ የሆነ o     በ እግዚአብሄር አብ የሆነ o     ከሰዎች ያልሆነ o     በሰዎች ያልሆነ   ጳውሎስ ገላትያ ክልልን ለቅቆ ከሄደ በኋላ ፈናቲክ(ኤክስትሪሚስት) “ጭፍን” አመለካከት ያላቸው   አይሁዳውያን በቤት እምነቶቹ መግባታቸው በክርስቶስ እየሱስ የሚገኘውን  ነጻ የጽድቅ ትምህርት   በማጣመም በሃይማኖታዊ ጥበብ እና ስራዓቶች በመቀየጥ ንጹሁን ወንጌል መበረዛቸው ነበር መልዕክቱን ለመጻፍ ያነሳሳው። ወንጌሉ  በአነሳሱ ሃይማኖታዊ ስራዓቶችን እየደገፈ እያበረታታ የመጣ ሳይሆን ፈንቅሎ የወጣ እንግዳ ነገር ነው። በሃይማኖታዊና ማህበራዊ ስራዓቶች የነበረውን ተቀባይነት ያለው ድርጊት፤ ባህል እና ስምምነት የናደ ታላቅ አብዮት ነው። ወንጌሉ በዚህ ዓለም ክስ ቀርቦበታል። ወንጌሉን  በ እግዚአብሄርና በሰው ላይ የተነሳ ምድርን የወረረ እጅግ ክፉ ወረርሽን ነው ትል ነበር አለም። በሌላ መልኩ ወንጌሉ ለዓለም በክርስቶስ እየሱስ የሚሆንን ድነት ፤ የህሊና ሰላምን እና በረከትን አምጥቷል።   ዓለም የጠላችው በዚህ ምክንያት ነው። እነዚህ ወግ አጥባቂ ጭፍን አይሁዳውያን   ·         ትክክለኛ የአብርሃም ነገድ መሆናቸውን ·         እውነተኛ የኢየሱስ ክርስቶስ አገልጋይ መሆናቸውን ·         በእውነተኞቹ ሃዋርያት የተማሩ መሆናቸው ·...

የገላትያ መጽሐፍ ጥናት 1

Image
ታሪካዊ ዳራ በመጀመሪያው ክፍለ ዘመን፣ በቤተክርስቲያን አብዛኞቹ ቀደምት ክርስቲያኖች አይሁዳውያን የነበሩ ሲሆን በሃይማኖት ወጎችና በጁዳይዝም ህግጋት ሞግዚትነት ስር እያደጉ ያሉ ሰዎች ነበሩ፡፡ ሆኖም እነዚህ አይሁዶች ክርስቶስን መከተል ሲጀምሩ፣ ከእግዚአብሔር ጋር የነበሯቸው ግንኙነቶች ተለወጡ፡፡ ከዚያም በክርስቶስ አማካይነት የእግዚአብሔርን ሙሉ መገለጥ ስላገኙ ወደ መንፈሳዊ በሳልነት የሕይወት እርከን አደጉ፡፡ ሆኖም ጥቂት ቆይተው፣ እነዚህ ቀደምት አይሁዳውያን ክርስቲያኖች የለመዱትን የአሮጌውን የአይሁድ ልምምዳቸውን ሲያጡ ምቾት አልሰማ ይላቸው ጀመር፣ ስለዚህ የክርስትና እምነታቸውን አሁን እየተዉት ካለው አይሁዳዊ ልማዳቸው ጋር መቀየጥ ጀመሩ ሌሎችም ያንኑ እንዲያደርጉ ያስገድዱ ጀመር፡፡ 1.        አይሁዶች ለ ክርስትና ቀደምት (ጀማሪዎች ) ናቸው 2.       አይሁዶች በይሁዲ ትምህርትና ስራዓት ያደጉ ናቸው 3.       በአዲሱ እና በቀደመው ህይወት መካከል የተፈጠረ ጥል 4.      በልማድ የተቀየጠ ወንጌል መፈጠሩ ጸሃፊው፡ ሀዋርያው ጳውሎስ ሚሲዮን ነበር።          ፡ ሚሲዮን ከመኖሪያ ሃግሩ ውጪ የተላከ መልክተኛ ነው።          ፡ ሚስዮን ልዑክ ማለት ነው።   የገላትያ አብያተክርስቲያናት የነበሩበት ሁኔታ ምን ነበር   የአህዛብ መብዛት   ሀሰተኛ መምህራን መበራከታቸው

የአንባቢዎች ብዛት